በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን!
ስንክሳር ማለት የእግዚአብሔርን ረድኤት አጋዥ በማድረግ በበጎ ስጦታውም የተሰበሰበ ማለት ነው.
ይህ ሃይማኖቶታቸው የቀና የከበሩ አባቶች, ከቅዱሳን ሰማዕታት, ከጻድቃን, ከነቢያት, ከሐዋርያት, ከሊቃነ ጳጳሳት, ከኤጲስቆጶሳት, ከመነኮሳትም ሁሉ ከገዳማውያንም ከገድሎቻቸው ከመላእከት አለቆችም ከድርሳናቸው የሰበሰቡትና ያቀነባበሩት አምላክን የወለደች እመቤታችን የከበረች ድንግል ማርያም ከአደረገቻቸው ድንቆች ተአምራቶችም የክብር ባለቤት የሆነ የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የበዓላቶቹን መታሰቢያ በዘመናት ሁሉ ከመስከረም መባቻ እስከ ዓመቱ ፍፃሜ ሁል ጊዜ ምእመናን እንዲያነንዲያነቡት እንዲሰ
ይህንንም ቅዱስ መጽሐፍ ሰብስበው ያቀነባበሩት በሽህ ሦስት መቶ ንጹሐን በሆኑ ሰማዕታት ዘመን ነው. የእሊህ የተባረኩ አባቶቻችን ጸሎታቸውና በረከታቸው ከእኛ
ለዘላለሙ አሜን!!
የቅዱሳንን ታሪክ ለማንበብ ከታሪካቸውም ለመማር እኛም በክርስትና ህይወታችን እንዲሁም በእለት ተእለት የኑሮ እንቅስቃሴያችን ውስጥ በዋነኝነት ቅዱሳኑ እንዲራዱን እንዲያማልዱንም በሌላም መልኩ ከነሱ የክርስትና ህይወት በመነሳት እኛስ ምን ማረግ እንችላለን ከቅዱሳኑ ታሪክ ምንን እማራለው የሚለውን እንድናስብ ይረዳናል ብሎ በማሰብ እንዲሁም በብዙ መፅሃፈ ስንክሳርን ማግኘት በማይችሉ ምእመናን ጥያቄ መሰረት ይህን የሞባይል አፕሊኬሽን ለራሶ እንዲሁም ከጉዋደኞቾ, ቤተሰቦቾ, የስራ ባልደረቦቾ ባጠቃላይ ከወዳጅ ዘመዶቾ ጋር በመሆን ይጠቀሙበት ዘንድ ትልቁን የቤተክርስቲያን መፅሃፍ መፅሃፈ ስንክሳርን ጠቅለንም ባይሆን ፈጣሪ በፈቀደ የቻልነውን ሙሉውን ታሪክ ያልቻልነውን ደግሞ ዋና ታሪኩን ጨምቀን አቅርበናል.
እርሶም እኝህን መንፈሳዊ ታሮኮች ሰአት መድበው በቀን ቢያንስ ከ3-10 ደቂቃ ወስደው የእለቱን ስንክሳር , እንዲያነቡ እንዲማሩበት ከወዳጆቾ ጋርም ውይይቶችን እኒዲያረጉበት እንመክራለን.
በዚህ አፕሊኬሽን ውስጥ የተካተቱት ብዙሃኑ ቅዱሳን ከ 6 ቱ እህታማማች ኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ አብያተ ክርስትያናት ናቸው
እነዚህም አብያተ-ክርስትያናት:-
- የ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
- የ ግብፅ / አሌክሳንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያኮፕቲክ ኦርቶዶክስ
- የ ሶሪያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን
- የ አርመንያ ሐዋርያዊ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን
- የ ኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
- የ ህንድ - ማንካራ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን
ያንብቡ ያነበቡትንም ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር በመሆን ይወያዩበት - አፕሊኬሽኑንም ለሌላቸው ያካፍሉዋቸው
ድጋፍዎ አስተያየትዎ አይለየን
ፈጣሪ ከቅዱሳኑ ይደምረን
አሜን!!
በዚህ እለት ማን ቅዱስ እንደሚከብር ያውቃሉ? ከነ ታሪካቸው ገብተው ይመልከቱ ከበረከታቸውም ተካፋይ ይሢ ይህንንም ስራ ሰርቶ ለማጠናቀቅ አመታትን የፈጀ ሲሆን በዚህ ስራ ላይ አብዛኞቹን ፅሁፎቹን በማዘጋጀት የላቀ ሚና ለተገበረው ለዲ / ን ዮርዳኖስ አበበ ምስጋናችን ከልብ ነው.
ዲ / ን ዮርዳኖስም ለብዙ አመታት እድሜውን ሙሉ መንፈስ ቅዱስ ባቀበለው መጠን ጎንደር በሚገኘዉ በዝክረ ቅዱሳን ጉባኤ የቅዱሳን ታሪክ በመማር, በማንበብ, በመተርጎም, በመፃፍ, በማዘጋጀት እና በማስተማር ጭምር የኖረ የቤተክርስቲያናችን አገልጋይ ነው. ይህንንም እርሱ ያዘጋጃቸውን ፅሁፎች በነፃ ምዕመንን ለማስተማር በፌስ ቡክ, በቴሌ ግራም እንዲሁም ለኛም በነፃ ሰጥቶን እኛም ዘመኑን በሚዋጅ መልኩ ህዝበ ክርስቲያኑን ለማስተማር እና የቅዱሳን በረከትንም ለኛም ላንባቢውም እንድንካፈል በአፕሊኬሽን መልክ አቅርበናል.
ስንክሳር * Sinksar – (Šventųjų gyvenimai) amharų ir anglų kalbomis.
ስንክሳር(የቅዱሳን ታሪክ) ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ Tewahedo ortodoksų stačiatikių bažnyčia Sinksar (Sinaksariumas)
Vardan Tėvo, Sūnaus ir Šventosios Dvasios, vienas Dievas Amen!
Norint pasimokyti iš Sinaksariumo ar istorijos ir krikščionių šventųjų gyvenimų bei tobulėti savo krikščionybėje, ypač stačiatikių Tewahedo bažnyčios gyvenime, labai rekomenduojame perskaityti knygą, o tiems, kurie negalėjo prieiti prie knygos čia yra jai skirta programa, kurioje yra pagrindinės istorijos su istoriją iliustruojančiomis nuotraukomis.
Dauguma šventųjų yra iš Rytų ortodoksų bažnyčios.
Šią Rytų ortodoksų komuniją sudaro šešios autokefalinės bažnyčios:
- Etiopijos ortodoksų Tewahedo bažnyčia,
- Aleksandrijos koptų ortodoksų bažnyčia,
- Antiochijos sirų ortodoksų bažnyčia,
- Armėnijos apaštalų bažnyčia,
- Eritrėjos ortodoksų Tewahedo bažnyčia ir
- Malankaros ortodoksų sirų bažnyčia.
- Amharų ir anglų kalbomis.
Skaitykite toliau, aptarkite tai, ką perskaitėte su kitais krikščionimis, ir toliau dalinkitės programa visiems pasaulio krikščionims.